#ባህል የሚለው ቃል የመጣው ከጥንታዊ....ቋንቋ "ቢል" ከሚል ቃል ሲሆን ትርጉሙም ሥራ ማለት ነው። "ቢል" የሚለው ቃል በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ ከአንዛ የአርኪኦሎጂ ሳይት በቁፋሮ ከተገኘ ጥንታዊ የድንጋይ ላይ ጽሑፍ ተቀርጾ ተገኝቷል። በደቡብ አረቢያ ደግሞ በቁርዓን የተጠቀሰውን ግድብ የገነቡ ሰዎች ተግባራቸው "ቢል" ተብሎ የተጠቀሰበት የታሪክ ማስረጃ ተገኝቷል። በሁሉም ቦታ "ቢል" ማለት ትርጉሙ ሥራ ነው። አሁን ይህቺ ቃል አሳስባኝ ሳይሆን ታሪካችን ትንሽ መልኩ ለወጥ እየተደረገ እንዴት በየቦታው ተሸፋፍኖ እንደሚገኝ በዚህ ምሣሌ ለመጠቆም ነው።

ቢል የሚለው ቃል ወደ ባህል ከተቀየረ በኋላ ባህል የሚለው ቃል ብሂል ከሚል የግዕዝ ቃል መጣ ይሉሃል። እሺ ብለህ ትማራለህ።  "ቢል" የሚለው ቃል ይረሳል። "ቢል" ድንጋይ ላይ በተቀረጸበት ዘመን ግን ግዕዝ የሚባል ቋንቋ ከቶ ህልው አልነበረም።

ሌላም ምሳሌ➟ዜና መዋዕል ማለት የውሎ ዜና ማለት ነው። "መዊል" የሚለው ቃል ወደ መዋዕል ከተቀየረ ሌላ ቋንቋ ነው የሚመስልህ።

➟ሌላም ልጨምርልህ። መስከረም ይባላል። ከሁለት ቃላት ጥምረት የተፈጠረ ቃል ነው።። መስ እና "ከርም" ከሚሉ። መስ ማለት አለፈ ማለት ነው። "ከርም" ደግሞ ክረምት ማለት ነው። መስከረም ሲባል ክረምት አለፈ ማለት ነው። ለስንት ዓመታት መስከረም የሚለውን ቃል እናውቀዋለን። ነገር ግን በዚህ ቃል ውስጥ "ከርም" የሚል ስልጥኛ ቃል እንደተደበቀ ጠርጥረን አናውቅም።

➟ሌላ ደግሞ። አብዛኛውን አማርኛ ቋንቋ የሚያውቅ ሰው ሀገር ወይም አገር የሚለውን ቃል ትርጉም ብንጠይቀው አይነግረንም። የዚህን ቃል አመጣጥ ለማወቅ ከግዕዝም በፊት የነበረ አንድ ጥንታዊ ቋንቋ ማወቅ ይጠይቃል። በዚያ ጥንታዊ ቋንቋ "አ" ማለት አበው፣ ቀደምት፣ ጥንታዊ...የሚል ትርጉም ነበረው።

ለምሳሌ➟አሰብ የሚለው ስም አ+ሰብ ነው። አ ቀደምት አበው ሲሆን ሰብ ደግሞ ሰው ማለት ነው። አሰብ ማለት ደግሞ ቀደምት ሰው ወይም አበው ማለት ነው።

አጋዝ➟አ+ጋዝ➟ቀዳሚ ዘማች ማለት ነው

አገር➟አ+ጋር➟ "ጋር" ማለት ቤት መኖሪያ...ማለት ነው። አጋር ማለት የአበው ቤት ወይም የቀደምቶች መኖሪያ ማለት ነው።

.

.

.

➟ሌላም ምሣሌ። ወር የሚል አማርኛ ቃል አለ።  ለ30 ቀን የተሰጠ ስም ነው። ወደ ስልጥኛ ና። ጨረቃ "ወሪ"(moon) ትባላለች። ጨረቃ ዞራ አንዴ ሙሉ ጨረቃ የምትሆንበት ክፍለ ጊዜ "ወሪ"(month) ተብሎ ይጠራል። ቀጥታ ከዘመን አቆጣጠሩ የተቀዳ ስያሜ ይህ "ወሪ" ነው። በግዕዝም ሆነ በአማርኛ ወር ሲባል የ30 ቀን ምድብ ስያሜ እንጂ ጨረቃ ማለት መሆኑን ምናልባት ከቤተክርስቲያን ካህናት በቀር አያውቁትም። ቤተክርስቲያን ከአሌክሳንደሪያ አምጥቶ አሻሽሎ የሚጠቀመው ዘመን አቆጣጠር ደግሞ የጨረቃ አቆጣጠርን የሚከተል አይደለም። "ወሪ" የሚለውን ቃል ወስዶ "ወር" በማድረግ ለ30 ቀን መጠሪያ ይጠቀማል። ትርጉሙ ግን ጨረቃ ማለት ነው።

.

.

.

.

እዚህ ጋር ስለቃላት ምንጭና ትርጓሜ ለመናገር አይደለም። ልክ ቃላቶቹ Remix ተደርገው ሲቀርቡልህ በፍጹም የራስህ እንደሆኑ ሳትጠረጥር ከሌላ ተቀብለህ ተምረሃቸው ትናገራቸዋለህ ትጽፍባቸዋለህ። ልክ እንደዚያ ሁሉ የራስህ ታሪክ Remix ተደርጎ በሌላ በኩል ሲቀርብልህ በአድናቆት የእገሌን ታሪክ ከማንበብ ውጭ እዚያ አካባቢ በፉጹም የተፐወዘ ያንተ ታሪክ ይኖራል ብለህ አትጠረጥርም። የፐወዙት ደግሞ ተራ ሰዎች አይምሰልህ። ትልልቅ ሊቃውንት ሥራዬ ብለው ይሄን የመፐወዝና አቅጣጫ የማሳት ሥራ ሲሰሩ ኖረዋል። ጠያቂና ፈላጊ ትውልድ ወደፊት እንደሚመጣ ቀድመው ማሰባቸው ይደንቃል። ታዲያ ሊቃውንት አቅጣጫ አሳስተው የቋጠሩትን የታሪክ ቋጠሮ ጫፉን ፈልገህ አግኝተህ በወጉ ለመፍታት ይቅርና ጭራሽ አትጠረጥርም።

➟እንደዚህ ነው ያስቀየሱህ ከራስህ እንዳትግባባ።